Friday, February 5, 2010

ውሽት ነገሠ!

መስቀል አደባባይ- ሀዝባችን ተጠርቶ
ሕጻን ሽማግሌው ባልቴት እና አዋቂው-
ግልብጥ ብሎ ወጥቶ
የክብር እንግዶች- ከአውሮጳ ከእስያ
ከጎረቤት ሃገር- ጅቡቲ ኬንያ
የአማሪካው ቆንሲል- ሚስተርም ተገኝተው
ጳጳሱ ተጠርተው- ካህናት ቀድሰው
ቅባ-ቅዱስ ፈልቶ-በአናቱም አፍስሰው
አክሊል ተደፋለት- እምቢልታ ተነፋ
ሕዝብ ሠገደለት- ሥልጣን ክብሩ ሰፋ
ከበሮ ተመታ-ሆታውም ቀለጠ- እልልታ ተሰማ
ውሸት ንጉሥ ሆነ- ሰርቆት አልጋ ወራሽ-በአገሬ ከተማ።

እናም የእኛ ሰፈር- ትልቅ ሽማግሌ
አንቱ የተባሉት- ትናንት እና ዛሬ
በቁርባን ያገቡት- በክርስትናቸው
ይኸው በአደባባይ -ሲዋሹ ያዝናቸው።

መቸ ይኸ ብቻ- ሆነና ነገሩ
በሃሰት ተከስው- ተሰማና ፋይሉ
ደግነት ቅንነት- እስር ቤት ገቡ አሉ።

እንግዲህ ምን ይሉ- ዘመን ተቀየረ
ውሃ ሽቅብ አይፈስ- ሲባልም ነበረ
ዘመን ተገላብጦ - ውሸት ተከበረ።

ኑሯችን ሆነና- ከደሃው ቀምተን
እውነትን ንቀነው- ውሸትን አንግሰን
ወደፊት ለመሄድ - መራመድ አቃተን።

ዳግማዊ ዳዊት
የካቲት 2002 ዓ.ም.

1 comment:

Anonymous said...

We all Ethiopian are in bad sorrow about his holly abune Zena. His holly was great treasury asset for us, but no choice God takes him. It is beyound our control; on the other hand, it is a wake up call for other wise follow Ethiopians because the time to pray for our unity by reconciling all silly mistake and differences either in home land or abroad. We will see that no one is eternal it is the time to see our selves Please! please! your identity is Ethiopian where ever you go with precious Orthodox tewahido history on earth. All be think in open minded manner for this short life time to do good and love each other.

Thank you!
Solomon