Wednesday, September 15, 2010

ጥምረትን በተመለከተ ጥቂት ነጥቦች፤ ማስታወሻ ለልጅ ተክሌ (ታደሰ ብሩ)

መንደርደሪያ

ልጅ ተክሌ " ያጣነው ጥምረት አይደለም፤ ድፍረት ነው" በሚል ርእስ በጻፈው ተገርሜም አዝኘም አልወጣ ስላለኝ ጥቂት ማለት ፈለኩ። በተደጋጋሚ ሙከራዎች ስላልተሳኩ ትብብር፣ ህብረት፣ ግንባር፣ ቅንጅት እና መሰል ቃላት ሁሉ የቫንኩቨሩን ልጅ ያንገሸገሹት ይመስላል። ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ያጣነው ጥምረት አይደለም ድፍረት ነው

ትብብር፣ ሕብረት፣ ግንባር፣ ቅንጅት፣ መድረክ፣ አሁን ደግሞ ጥምረት

ልጅ ተክሌ (ቫንኩቨር-ካናዳ)

አንዱ ይሄ ቀጥዬ የምተቸው ክስተት የማይጥመው ወዳጄ፡ “ትብብር መጣ፡ ሕብረት መጣ፡ ቅንጅትም መጣ፡ መድረክም መጣ፡ እነሆ አሁን ደግሞ ጥምረት መጣ፡ እንግዲህ የቀረው ድብልቅ” ነው ብሎ ተሳለቋል። ከዛሬ ነገ አስመራ ገብቶ የግዞት መንግስተ ያቋቁማል ወይም አንዱን የሕወሀት ሚኒስትር አፍንጫውን ይለውና አንጀታችንን ያርሳል፤ እንደው ሌላው ቢቀር ባለበት ሆኖ በድፍረት እኛ ነን እንጂ እናንተ መንግስተ ልትሆኑ አይገባችሁም ብሎ ይናገራል ብዬ ስጠብቅ በዚህ ጊዜ አለን የምንለው ጠንካራው የፖለቲካ ድርጅት ግንቦት ሰባት፣ አንዱን ግንባር ወይም ትብብር በቅጡ ሳናጣጥም ሌላ ጥምረት የሚባል ፍጥረት ይዞ ሲድህብን በጣም ተበሳጭቻለሁ። እኔ ጸረ-ፓርቲዎች-ጥምረት ነኝ። የስራ እንጂ የፕሮግራም ትብብር አይመቸኝም።

የተግባር እንጂ የአመራሮች ህብረት አይጥመኝም። ጠላታችን ሕወሀትም ይሁን ወዳጃችን ሻእቢያ ያሸነፉን በማጥቃት ጥምረት ነው እንጂ በፕሮግራም ትብብር አይደለም ባይ ነኝ።

ነገሩ እንዲህ ነው። ነሀሴ 20/2002 የወጣ አንድ መግለጫና ዜና፤ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሕዝብ የአንድነትና የፍትህ ንቅናቄ ተቀናጅተው “ጥምረት ለነፃነት፣ ለእኩልነትና ለፍትህ በኢትዮጵያን” መስርተዋል ሲል ይናገራል።[1] መግለጫው የዚህን ጥምረት መፈጠር እንደዜናም እንደምስራች ያስቀምጠዋል። እኔ ግን ይሄ የምስራችነት የሌለው እንዲያውም ያው የተለመደውን የምንጠቃበትን ፖለቲካዊ አካሄድ የደገመና ፋይዳ ቢስ ፖለቲካዊ ርምጃ ነው ባይ ነኝ። ይሄ የጥምረት ምስረታ እዚህ ላይ ሳያቆም፤ ድርጅቶች አቅማቸውንና ጥረታቸውን አስተባብረው ቢሰሩ ወያኔን ለመጣል ስለሚረዳ ሁሉን አቀፍ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሀይሎች ህብረት ለማምጣት ይተጋሉ፤ ይሄም በግንቦት ሰባትና አጋሮቹ የተመሰረተው ጥምረት የዚያ ሁሉን አቀፍ ሕብረት የመመስረት እንቅስቃሴ መጀመሪያ ነው ይላል መግለጫው። ገና ሌላ ሕብረት፣ ሌላ ጥምረት፣ ሌላ ግንባር ይመጣል ማለት ነው። ትግሉ መንገድ ጠራጊ መጥምቁ ዮሃንስን መላክ ብቻ ሆነኮ ጎበዝ። ክርስቶስ አልመጣ አለን።

ሕብረት፣ ጥምረት፣ ክስረት ናቸው፡ የእብደት ስራዎች፦

እኔ የምለው ብዙ ነገር ቢሆንም አንዱ ግን ይህ ነው። ሰፊና ሁሉን አቀፍ ህብረት መመስረትና ማምጣት ወያኔን ከመጣልና ዴሞክራሲያዊ መንግስት ከመመስረት ጋር ምንም አያገናኘውም። እንዲያውም ከልምድ እንዳየነው ወያኔን ለመጣል ብቻ በግድ የሚመጣ ህብረትና ግንባር መጨረሻው ተስፋ በሚያስቆርጥና እንደገና ለመጣመር በሚያስቸግር መልኩ መፈረካከስ ነው ባይ ነኝ። እኔ ምን ሩቅ ወሰደኝ በኢትዮጵያ 18 አመት ታሪክ ውስጥ እንደ ህብረት፣ ጥምረት፣ ግንባር፣ ትብብር፣ ቅንጅት መፍጠር የሰለቸንና ትግላችንን የጎዳ ፖለቲካዊ ሙከራ የለም። ፖለቲካዊ ሙከራ ጥሩ ነው። ሰው ግን አንድን ነገር ሁልግዜ ሲሞክር አይኖርም። ሲሞክር አይሞትም።
እብደት ማለት አንድን ነገር በተመሳሳይ መልኩ ደጋግሞ መሞከርና የተለየ ውጤት መጠበቅ ነው ከተባለ ግንቦት ሰባትም ይሁን ሌሎቹ ድርጅቶች የሰሩት ጥምረት የመፍጠር ስራ የእብደት ስራ ነው። ተሞክሮ ተሞክሮ ያልሰራን ነገር ነው በዚያው በፊት በተሞከረበት መልኩ ነው የሚሞክሩት። ምንም አይነት የፖለቲካዊ ንጥረ ነገርም ይሁን የፖለቲካዊ ቀመር ለውጥ የለውም። በፊትም የተደረገው እከሌ እንቶኔና እከሊት የተባሉት ድርጅቶች ወያኔን በጋራ ለመጣል ሕብረት መሰረቱ ነው። አሁንም ያው ነው። ለውጡ የስም ብቻ ነው። ይሄ እንደ ትልቅ የምስራች ሊነግሩን የሚገባ ዜና አይደለም ባይ ነኝ። ላንዳንዶቻችን እንዲያውም ይሄ መርዶ አይነት ነገር ነው። ምክንያቱም ከዚህ ቀደም በሚፈጠሩ ትብብሮች ውስጥ ያየነው ተሞክሮ አንድም መፍረስ ሌላም የትም አለመድረስ ነውና፤ ደግሞ እንደገና ስንሳቀቅ ከምንኖር ባንሰማው ይሻል ነበር።

ጥምረትና ህብረትን የምጠላባቸው ምክንያቶች፡ አጉል ፉክክር ይፈጥራሉ

አንደኛ ነገር እንዲህ ያሉ ትብብሮች ወይንም ቅንጅቶች ጤናማ ላልሆነ ፉክክርና ፖለቲካዊ ሽኩቻ በር ይከፍታሉ። በድርጅቶቹ መካከል የተዛባ የሰው ሀይል፣ የአባላት ቁጥር እና የሀብት ስርጭት አለ። ያንን አስተናግዶና አቻችሎ መጓዝ እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነው። ይሄ ጥምረት፣ ህብረት፣ ትብብር ምናምን የሚባል ነገር እኛ ልጆች ሆነን በምንመኘው የየዋሀን ምኞትና መተማመን የተጎነጎነ የፖለቲካ ጨዋታ ነው። ፖለቲካ ውስጥ ውድድርና ፉክክር አለ። አንዱ ይበልጣል አንዱ ደግሞ ያንሳል። በአናሳዎችና በሀያላን መካከል የሚደረግ ሕብረት ወይም ጥምረት ሀያላኑ ዘወትር ስለስራቸው ሳይሆን እንዴት አድርገን አናሳዎቹን እናስደስት በሚል ደካማዎቹ ደግሞ እንዴት አድርገው ሀያላኑ ጥቅማችንን ጎዱ ወይም ጠቀሙ በሚል ጥያቄ የሚጠመዱበት ሂደት ነው። ይሄ ጥምረት አጉል ፉክክርና አጉል ሽኩቻ ይፈጥራል። ፖለቲካችን የራሱ በቂ ሽኩቻ እያለው እነዚህ ድርጅቶች እንደገና ጥምረት የሚባል ነገር ፈብርከው ሌላ ሽኩቻ ማከል አልነበረባቸውም።

ሕብረት የመፍጠር ትግል እንደ ግብ

ሁለተኛ ይሄ ህብረት፣ ትብብር፣ ግንባር፣ ቅንጅትን የምጠላበት ምክንያት እነዚህ ትብብሮች ወደግብ መድረሻ መንገድ ሆነው ሳለ በራሳቸው እንደ ግብ ወይም እንደ ስራ እየተወሰዱና በርግጥም ስራ ለመስሪያ መስሪያ ሳይሆኑ ድክመትን ለመሸፈኛ ዘዴ እየሆኑ ስለመጡ ነው። ግንቦት ሰባትን ወይንም በዚህ ጥምረት ውስጥ የተሰለፉትን ድርጅቶች ማለቴ አይደለም፤ ነገር ግን ብዙ ድርጅቶች የተቋቋሙለትን ስራ መስራት ሲሳናቸው፡ ህብረት መፍጠርን እንደ ስራ ያዩትና ህብረት ወይንም ግንባር ወይንም ትብብር ፈጠርን ብለው እንደ ተጨማሪ ጥቂት ወራት ማግኛ ወይንም ግዜ መግዣ የሚጠቀሙበት የፖለቲካ ግርግር ሆኖብኛል። ግንቦት ሰባት ከተቋቋመ ግዜ አንስቶ ብዙ ስራዎችን ለመስራት የሚሞክርና የሰራ ድርጅት ቢሆንም፡ ከዚህ ከላይኛው ክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ ሊሆን ግን አይችልም።

ቀድሞውንስ ሶስት አራት ለመሆን ምን ምክንያት አለን?

ሶስተኛው ምክንያቴ፡ ቀድሞውንም ነገር አንዳንድ ድርጅቶች የተለያዩ ድርጅት ለመሆን ምንም አይነት አጥጋቢ ምክንያት ሳይኖራቸው ብቻ በኩራት የቆሙ መሆናቸው ነው። ለምሳሌ የአፋር ወይም የኦሮሞ ወይንም የሲዳማ ድርጅቶች የወጡበትን ብሄር ብቻ መሰረት ያደረገ ጥያቄና አጀንዳ ሊኖራቸው ይችላልና ሰማኒያ አምስት የብሄር ድርጅቶች ቢፈጠሩ አይገርመኝም። ነገር ግን በዚህ አሁን በተፈጠረው ጥምረት ብንሄድ፡ የግለሶበች ጸብና ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር የተቀሩት ሁለት ድርጅቶች ህብረ-ብሄራዊ አጀንዳቸው ተመሳሳይና ብሄርን ሳይሆን ኢትዮጵያን መሰረት ያደረገ ፍላጎት ያላቸው ናቸው። አንዱ የኢትዮጵያ አንድነትና ፍትህ ንቅናቄ ነው። አንዱ ደግሞ የነጻነት፡ የፍትህና የነጻነት ንቅናቄ ነው። ስለዚህ የስልጣን ይገባኛል ጥያቄ ካልሆነ በስተቀር ከግንባር ወይም ጥምረት ይልቅ አጀንዳቸውን አስተካክለውና አስማምተው ውህደት የማይፈጽሙበትና እንደ አንድ ውህድ ድርጅት የማይቆሙበት ምክንያት ምንድር ነው? ምንም። የብሄር ድርጅቶቹን እንተዋቸውና፡ ከኢትዮጵያ ጋር በተያያዘ ነአምን ዘለቀን ከዶ/ር ብርሀኑ ምንም የሚለየው መሰረታዊ ነገር ስለሌለው ሁለት ድርጅት አያስፈልጋቸውም። ሁለቱም ባንድ ድርጅት ታቅፈው መንቀሳቀስ እየቻሉ፡ የምንታገለው ለኢትዮጵያ አንድነት ነው እያሉ እንደገና ደግሞ ሁለት ሶስት ድርጅት ውስጥ ሙጭጭ ብሎ ጥምረት፣ ትኩረት፣ ምናምን እያልን ጊዜና ጉልበት የምናባክንበት ምክንያት አይታየኝም።

ስጋቴ ምንድን ነው? በፍትወት የሚቃጠል መነኩሴ አይነት ነገር

ስጋቴ እንደሚከተለው ነው ትብብር ማለት ሁሉም የራሱን የድርጅት ፍቅር ሳይገድል፣ የራሱን ጥቅምና ፍላጎት ይዞ የሚመጣበት፤ በኋላ በጋራ ከሚሰራው ስራ በይበልጥ የራሱን የድርጅት ጥቅም አስቀድሞ እኔ ምን አገኛለሁ የሚለውን ነገር የሚያስብበት አወቃቀር ነው። ለዚህ ከቅንጅት የተሻለ ተሞክሮና ከዶ/ር ብርሀኑ የተሻለ ምስክር የለም። እሱ ራሱ በጻፈው የነጻነት ጎህ ሲቀድ በተሰኘ መጽሀፉ ቅንጅትን ለመፍጠር ከተፈጠረም በኋላ ቅንጅትን ለመጠበቅ የነበረውን መከራና ፈተና አሳይቶናል። ትብብር፣ ቅንጅት፣ ግንባር፣ ህብረት ምናምን የሚባሉ ነገሮች የወሲብ ስሜቱን ሳይገድል እንደሚመንኮስና በኋላ በፍትወት እንደሚቃጠል መነኩሴ ይመስሉኛል። ድርጅታዊ ፍትወታቸውን ይዘው ጥምረት ይመሰርታሉ፡ በሁዋላ በድርጅታዊ ፍትወታቸው ጥምረቱንና ትግሉን ያምሱታል።

ለነገሩ ወደታች በሰፊወ እወርድበታለሁ፤ እኔ የምለው ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት የፓርቲዎች ውህደት ከዚያ መለስ ደግሞ ሁሉም የራሱን ስራ ብቻ እንዲሰራና ርስ በርስ እንዳይጠቃቃ የሚይዝ ስምምነት ነው እንጂ ወራትና አመታት የሚፈጅ የድርጅቶች ጥምረት ወይንም ትብብር ምስረታ አይደለም። ድርጅቶች የፈጀውን ጊዜ ይፍጅ፤ ወደ ውህደት ማምራት ነው ያለባቸው። የብዙሀን ፓርቲ ስርአትን መቃወሜ አይደለም ነገር ግን ድርጅቶች መዋሀድ ካልቻሉ፡ ሁለተኛ ማድረግ የሚችሉት ነገር፡ ሁሉም ድርጅት ስራዉን እንጂ የሌላውን ድርጅት ስራ እንዳይነቅፍ፣ ትኩረቱ የጋራ ጠላት ላይ እንጂ ርስ በርስ እንዳይሆን ብቻ የጋራ ስምምነት ላይ መድረስ እንጂ ጥምረት፣ ሕብረት፣ ትብብር ምናምን የሚባሉ ነገሮች ግርግር ለመፍጠርና ላንድ ቀን ዜና ፍጆታ ብቻ የሚውሉ ምንም አይነት ዘላቂ ፖለቲካዊ ፋይዳ የሌላቸው ፍጥረቶች ናቸው።

የግንቦት ሰባት ርእሰ አንቀጽ

ግንቦት ሰባት ድርጅት በሴፕቴመበር 3 ርእሰ አንቀጹ እንዳለው ይሄ ጥምረት “የተደራዳሪዎችን ቁጥር ከመቀነስ ውጪ” ምንም አይነት የላቀ ሚናና ፋይዳ አይኖረውም።[2] የግንቦት ሰባት ርእሰ አንቀጽ ከአሁን ቀደም ከተመሰረቱ ህብረቶች ዘላቂነት ማጣት አንጻር ከዚህ በኋላ የምንመሰርተው ህብረት ያለፉትን ስህተቶች የሚደግም መሆን የለበትም ይላል። ጥምረት የሚባል ነገር መፍጠሩና እንደትልቅ ድል ማብሰሩ በራሱ ትልቅ ስህተት መድገም ነው። አንደኛ ነገር ይህ ጥምረት ያለፉትን ህብረቶች ስራ ከመድገም ውጪ ያደረገው ወይም የሚያደርገው ምንም አይነት የተለየ ነገር ሊገለጥልኝ አልቻለም። ከዚህ በፊት የነበሩት ጥምረቶች ችግር ትኩረታቸው ዓላማቸውን እንዴት እናሳካዋለን የሚለው ነጥብ ላይ ሳይሆን እንዴት ስልጣን እንደላደል ነው። ማን ጸሀፊ፣ ማን ሊቀመንበር፣ ማን ምክትል ይሁን አይነት ነገር። በዚህ ጥምረት የስልጣን ድልድል ተደረገ። አንዱ ድርጅት ሊቀመንበር፣ አንዱ ደግሞ ምክትል፣ አንደኛው ደግሞ ጸሀፊ ሆነ። ከዚያ መለስ ሌላ ምንም ነገር የለም። በቃ የጥምረቱ ስራ እዚያ ጋር አበቃ። ከዚያ ፈቀቅ ሊል አይችልም። ቀጥሎ የምንሰማው አንዱ ድርጅት ሌላኛውን ድርጅት ሲከስ ነው።

ስላልን ብቻ የሚሳካ ነገር የለም፤ እንዲያውም ግርግር ይፈጥራል

ግንቦት ሰባት ወይም አሁን የተፈጠረው ጥምረት “ከዚህ በፊት የተፈጠሩ ህብረቶች የነበረባቸውን ድክመት በማረም አሁን የሚፈጠረው ወይንም የተፈጠረው ህብረት ከሌሎቹ በተሳካ መልክ ይሰራል” ስላለ ብቻ የሚሳካ ነገር የለም። ጥምረቱ የፖለቲካ ድርጅቶች ጥምረት፤ ተባባሪዎቹም ፖለቲከኞች ናቸው። ከዚህ በፊት ከነበሩት ጥምረቶች ምንም የተለየ የሚያደርገው ነገር የለም። ፖለቲከኞቹም ከዚህ በፊት ተሞክረው በነበሩ ትብብሮች ውስጥ በተለያዩ መልኩ ሰርተው የተሳካላቸውም ያልተሳካላቸውም ፖለቲከኞች ናቸው። ስለዚህ ያው የቀደሙትን የመተባባርና የመገነባበር ጥረት የሚደግም እንጂ የተለየ የሚያደርገው ነገር የለም። እንደውም የዚህ ጥምረት መምጣት ሌላ የሚፈጥረው ግርግር አለ። የስያሜዎች መብዛት በህዝቡ ውስጥ ግር መሰኘትንና ግራ መጋባትን ይፈጥራል። የዚህ ህብረት፣ የዚያ ግንባር፣ የዚህ ቅንጅት፣ የዚያ ትብብር፣ የዚህ መድረክ። አሁን ዝርዝሩም ሊጠፋን ነው። ጓደኛዬ እንዳለው ቀጥሎ ድብልቅልቅ ሊመጣ ነው።

ነጥቤን ረሳሁት፤ ስንተኛ ላይ ነበርኩ? የሚያስፈልገን ድፍረት ነው

ሰባተኛ ይሁን ስምንተኛ እንጃ ብቻ ጎበዝ እንዲያውም ጥምረት፡ ክስረት ነው። ጊዜና ገንዘብ ሰውም ይበላል። ልብ አድርጉ ሕወሀትን ለመጣል የተቃዋሚዎች ሕብረት ያስፈልጋል ካልን፡ ይሄንን ጥምረት ለመፍጠር ደግሞ ድርድሩ ከአንድ አመት በላይ ከፈጀ፡ ሁሉን አቀፍ ሕብረት ለማምጣት ደግሞ ስንት አመት እንደሚፈጅ አስቡት። ይሄ ጊዜ ማባከን ነው። ዝም ብሎ ስራን መስራት ይሻላል። ሁሉም እየሰራ እየሰራ እየበረታ ሲሄድ ድርጅቶች ራሳቸው እንቀላቀል ብለው ይመጣሉ። እንጂ በባዶ ሜዳ ጥምረት ለመፍጠር አንድ ወርቅ አመት ማባከን የፖለቲካ ቅንጦት ነው። አሁን ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ድርጅቶችን ሕብረት ለማምጣት ሌላ ሶስት አራት አመት የሽግግር መንግስት ለማቋቋም ደግሞ ሌላ አምስት አመት። ይሄንን ሁሉ ጊዜ ኢትዮጵያና ኢህአዴግ ቁጭ ብለው ይጠብቁናል። ግንቦት ሰባት የሚበጀውን ያውቃል። ግን እንደኔ እንደኔ ዝም ብሎ ስራውን እየሰራ ሌሎቹም ስራቸውን እየሰሩ አንድ ቀን ያለላቸው እለት ቢዋሀዱ ይሻላቸው ነበር። ለነገሩ እኛ የሚያስፈልገን ጥምረት አይደለም፡ ድፍረት ነው።

ምሳሌ ዶ/ር ብርሀኑ እና ግንቦት ሰባት

ሌላ ምሳሌ አሁን ዶ/ር ብርሀኑ እንደምንድን ነው የሚናገረው? እንደ ግንቦት ሰባት መሪ? እንደ ጥምረቱ መሪ? ይሄ የጥምረቱ ሃሳብ ነው፤ ይሄ ደግሞ የግንቦት ሰባት እምነት ነው እያልን ስንታገል ልንኖር ነው። ለደጋፊዎቹና ለተከታዮቹ እንዲሁም ለተመልካቾቹ የቤት ስራ የሚያበዛ ጥምረት፡ ክስረት ነው። በተለይ በኢትዮጵያ ስም የሚመሰረቱ ድርጅቶች የራሳቸውን ድርጅት ጥቅም ለማስጠበቅ የሚራኮቱበት ትብብር ከመፍጠር ይልቅ እንደምንም አላማቸውንና ፕሮገራማቸውን አፋጭተው አንድ ፕሮግራም ፈጥረው ውህደት የሚመሰርቱበት እድል ለመፍጠር ነው መታገል ያለብን። ከዚያ በሁዋላ እንደ አፋር ያሉትን በብሄር ላይ የተመሰረቱ ድርጅቶችን በጋራ መስራት በምንችልባቸው ሁኔታ ላይ የምር ማወያየት። ከዚያ በተረፈ ግን አሁን የአፋር፣ ከዚያ ደግሞ የኦሮሞ፡ የኦጋዴን የእከሌ የሚባሉትን ድርጅቶች የምናስገባቸው፤ ለይምሰልና ለታክቲክ ብቻ የድርጅትንና የትግልን መልክ ለማሳመር ይመስላል።

ግንቦት ሰባት ምን ነካው?

በሌላ አነጋገር እኮ፡ የግንቦት ሰባት አዝማሚያ፡ እኔ ጎዶሎ ነኝ፡ አጀንዳዬም የኢትዮጵያን ህዝብ ሁሉ አይወክልም የማለት ፈራ ተባ የማለት ነገር ነው። ስለዚህም በጥምረት ስም ክስረት የመጋበዝ ያህል ነው ያየሁት አካሄዱን። ግንቦት ሰባት አጭር እድሜ ቢኖረውም ብዙ ሰዎችን በሙሉ ግዜ የሚያሰራና በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ በአለማችን የተለያዩዩ ክፍሎች ብዙ አባላትንና ደጋፊዎችን ማፍራት የቻለ ትልቅ ድርጅት ነው። በተቃራኒው ሌሎቹ ጥምረቱን የመሰረቱ ድርጅቶች በሰው ሀይል ብዛታቸውም ይሁን በሀብታቸው ብዛት አናሳ ይመስላሉ። አንዳንዶቹ መኖራቸውንም አናውቀውም ነበር። እንዲያውም መኖራቸውን ራሱ የሰማነው ጥምረት መሰረቱ ሲባል ነው። ያ ይሁን፡ ቢያንስ እነዚህ ድርጅቶች ለአባላቶቻቸው ነበሩላቸው። ዋናው ችግሬ ግን ይሄ ጥምረት በሚታወቁና በማይታወቁ ድርጅቶች ሲመሰረት፤ የሚታወቁት ድርጅቶች በስራቸው ሳይሆን በመሰረቱት ጥምረት ብቻ ከታወቁ በሁዋላ ጥምረቱ ለስራ ሲንቀሳቀስ ከዋንኛው የአገሪቱ ጉዳይ ይልቅ ሜካኒካል የሆኑ የስልጣንና የምክክር ጉዳዮች ላይ ብቻ በማተኮር ድርጅቶቹ ርስ በርሳቸው ፉክክር እንዲያደርጉና እንዲካሰሱ መንገድ ይፈጥራል የሚለው ነው። ከዚህ በሁዋላ እነዚህ በስራቸው ሳይሆን በጥምረቱ መመስረት ምክንያት ያወቅናቸው ድርጅቶች በዚህ ጥምረት መመስረት ምክንያት ምንም አይነት ችግር ለመፍጠር አቅም ያገኛሉ። ጥምረት በስራ ላይ ለውጥ ስለማምጣቱ ዋስትና የለንም ችግር ስለመፍጠሩ ግን ካለፈው ልምድ ተነስተን በርግጠኝነት መናገር እንችላለን።

ሌላ ምሳሌ፡ የቅንጅት ነገር

የቅንጅት ምስረታ አንዱ ችግር ውስጣዊና ልባዊ አለመሆኑ ነው። መዋሀድ የማይችሉ ግለሰቦችና ቡድኖች በግድና ለምርጫ ሲባል ብቻ ተዋሀዱ ተባሉ። ስለዚህም ቀደም ሲል እንደ ድርጅት የነበራቸውን የግል አተካራና ፍትወት ሳይገድሉ ወደ ቅንጅትነት ሄዱ። ከነ ፍትወቱ እንደሚመለኩሰው መነኩሴ ነገር ማለት ነው። ከዚያ በሁዋላ የግልና የድርጅት ፍትወታቸውን መግደል አልቻሉም ነበርና ፓርቲ መሆን አልቻሉም ነበር። ፈረሱ። የህወሀት ተንኮልና አስተዋጽኦ እንደተጠበቀ ሆኖ ቀድሞውንም ቅንጅት በግድ የተሰባሰቡ ድርጅቶች ፍጥረት ነበርና ስራውን በድል ከማጠናቀቁ በፊት ለውድቀት በቃ። ሌላ ማን ነበር? ትብብር ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚባል መጣ (ኤ.ኤፍ.ዲ)። የት እንደገባም አናውቀውም። መድረክ አገር ቤት አለ ገና አልለየለትም። ብርቱካን እስር ቤት ገባች፡ ድርጅቷ አንድነትም አንዴ እንደመድረክ አንዴ እንደ አንድነት እየተንገዳገደ ሳለ፡ እነሆ አሁን ደግሞ እዚህ ጥምረት የሚባል ሌላ ፖለቲካዊ ጣጣ መጣ።

ጥምረት አልገባኝም፤ ይልቅስ ተዋሀዱ

የሚያስፈልገን ውህደት ነው። ከዚያ መለስ ሁሉም ዝም ብሎ ስራውን ይስራ። በቃ ስራውን ብቻ። በሌላው ስራ ጣልቃ አይግባ። ስራው ራሱ ጥምረቱንም ውህደቱንም ያመጣዋል። በወያኔና ሻእቢያ መካከል ተፈጠረ የሚባል ጥምረት፣ ግንባር ምናምን የሚባል የፕሮግራም ትብብር አላስታውስም። የስራ ትብብር ነበር የነበረው። ያም ሻእቢያነቱን ጠብቆ፡ ይሄም ሕወሐትነቱን ጠብቆ ጠላታችን የሚሉትን ደርግን ያጠቁ ነበር። የስራ ውህደት ነበር። አንዱ ላንዱ ትጥቅና ስንቅ ያቀብላል። አንዱ ላንዱ ደጀን ይሆናል። አንዱ ላንዱ ይተኩሳል። በስራና በትግላቸው አንድ በተፈጥሮ ግን ሁለት ሆነው፡ አንድም ሁለትም ሆነው ስራቸውን ሰሩ። ያንን ነው የምንፈልገው። አፋርም ስራውን ይስራ። ግንቦት ሰባትም ስራውን ይስራ። ኢህአፓም ስራውን ይስራ። ኦነግም ስራውን ይስራ። ከዚያ ስራው ራሱ የጥምረቱን አስፈላጊነት ያምጣው። ያለበለዚያ እንዴት ነው እዚያና እዚህ የሚረግጡ አላማና ድርጅት ይዘን ህብረት፤ ወይንም ትብብር ወይንም ጥምረት የምንመሰርተው? አይገባኝም።

አልጨረስኩም፤ አስራምናምንኛ ነጥብ አለኝ፤

አሁንም በጣም ይቅርታ እኔ ይሄ ህብረት፣ ጥምረት፣ ትብብር፣ ግንባር፣ ምናምን የሚባል ነገር በጣም የሚቀፈኝ ዋስትናም ስለሌለው ነው። የመጣላትና የመጋጨትም እድሉ ሰፊ ነው። መካሰስ ይኖራል። በተለይ እንደዚህ እንዳሁኑ ሶስት አቅማቸው የተዛባና የማይመጣጠን ሀይሎች ሲጣመሩ፤ የመጣላትና የመካሰስ እድሉ የሰፋ ነው። የአፋር ብድግ ይልና ግንቦት ሰባትን ሊከስ ነው። በስማችን ነገደ፣ ስልጣኑን ሁሉ ያዙት፣ ሳንመካከር ተሰራ፣ የሀብት ክፍፍል ፍትሀዊ አይደለም፣ ግንቦት ሰባት የራሱን ምልመላና ቅስቀሳ ብቻ ያጧጡፋል … በሽ የክስ ዝርዝር ሊመጣ ነው። ሌላኛውም እንደዚያ። የማን ሀብት የማን ሊሆን ነው? ግንቦት ሰባት እንደ ግንቦት ሰባት የለቃቀመውን መዋጮና ሌሎች ቁሶች እንዲሁም የሰው ሀይል ለብቻው ይዞ ሊጓዝ ነው ወይንስ እንዴት ያለ የመከፋፈያ ቀመር ሊፈጥር ነው። ነው ወይስ ትግሉ እዚያ ላይ ሊሆን ነው?

እቺ በጣም ጠቃሚዋ ነጥብ ነች፤

ጥምረት ወይም ትብብር ወይም ህብረት አደጋም አለው። ለነገሩ ጥምረቱ በትግላችን ላይ የሚጨምረው ነገር አለ ብዬ አላምንም። ቢኖርምና በጥምረቱ ድል እያደረግን ብንመጣም እንኩዋን ወያኔ የመጀመሪያው ርምጃው የጥምረቱ አካል የሆኑትን ሀይሎች ማባበልና የሚፈልጉትን ነገር መስጠት ነው። ለምሳሌ ግንቦት ሰባትና ወዳጆቹ ከኦነግና ከኦጋዴን ነጻ አውጪ ጋር ትብብር ወይንም ህብረት መሰረቱና በትግሉ እየገፉ ወያኔን የሚያሰጉበት ደረጃ ላይ ደረሱ እንበል። የፓርቲ ውህደትና አንድነት እስከሌለ ድረስና ሁሉም ድርጅት እንደ ድርጅት የያዘውን ዓላማ እስካልተወ ድረስ የተሻለ ስጦታ ከሚሰጠው ከማንም ጋር ለመስራት ምንምና ማንም አይከለክለውም። በዚህ ዘመን ለኦነግና ለኦብነግ አላማዎች፤ ከግንቦት ሰባት አይነት የአንድነት ሀይሎች ይልቅ እንደ ኢህአዴግ ያለ የብሄር ድርጅቶች ስብስብ የተሻለ የቀረበ ነው። ኢህአዴግ በብሄሮች መብት እስከ መገንጠል ያምናል። ግንቦት ሰባት በዚህ አያምንም። አከተመ። ግንቦት ሰባትና ኦነግ የሚፈጥሩት ህብረት በባህርዩ በጣም ስስና ዘላቂነቱ የሚያጠራጥር ነው። ስለዚህ እንደ ኦነግ አይነት ሀይሎችን በጥምረቱ ወይንም በትብብሩ ውስጥ እንዲቆዩ የሚያስገድዳቸው ምክንያትም ግዴታም የለም። ስለዚህ የዓላማ አንድነትና ውህደት ካልሆነ በስተቀር፡ ይሄ ጥምረት ምናምን የሚባል ነገር በመጨረሻ እያወቁ ክስረት ነው። አደገኛ ነው። ተክሌ ምን አለ ትላላችሁ አይሰራም። በሰራና እኔ ባፈርኩ።

ጎበዝ - እንደማጠቃለያ

ወያኔ በጥምረት አይደለም ያሸነፈን። ወያኔ ከድርጅታዊ ጥምረት ወይንም ከድርጅታዊ ግንባር ይልቅ በድርጅታዊ ጥበትና ሞኖፖሊ ነው ያሸነፈን። ሕወሀት እንደ ትግሬ ተደራጅቶ፡ እንደአማራ ጠላት ተሰብስቦ እንደ ትግሬ ጦር ተዋግቶ ነው ያሸነፈን (የትግራይ ህዝብ ለዚህ ተጠያቂ አይደለም)። እንደ ኢትዮጵያዊ ሀይል አይደለም ያሸነፈን። እንደ ሕወሀት መደራጀታቸው ረዳቸውና አሸነፉን። በመጨረሻ አካባቢ እስካሁንም ድረስ እን አባዱላ ገመዳንና እነ ታምራት ላይኔን ለቃቅመው እንደ ኢህአዴግ መደራጀታቸው ከትግሉ ይልቅ ቀጣዩን የመንግስትነት ጉዞ ለመጓዝ ነው የረዳቸው። እንጂ እንደ ህወሀት ነው ያሸነፉን። ካሸነፉን ደግሞ ካሸናፊዎች መማር አለብን። ከጠላትም ቢሆን። በወያኔ የትግል ታሪክ ውስጥ የስራ ጥምረትና ሕብረት እንጂ የነበረው የፖለቲካ ፕሮግራም ሕብረት አልነበረም። ጥንትም ሕወሀት ናቸው፡ አሁንም ሕወሀት ናቸው።

ከዚያ በተረፈ

እድሜያችን እየገፋ ሲሄድ ከፖለቲካ የተማርነው ነገር በምንም መልኩ አለመተማመንን ነው። ወይንም ፖለቲከኞች ቃላቸውን ይጠብቃሉ ወይንም እንደኛ ያስባሉ ወይንም ቅን ልቡና አላቸው ተብሎ ብቻ በማመን የሚሰራ ስራ አለመኖሩን ነው። ስለዚህ ገና ለገና ወደ ጥምረት የሚመጡ ድርጅቶች ሁሉ ከራሳቸው ጥቅምና ፍላጎት ይልቅ የአገርን ፍላጎት ያስቀድማሉ ብሎ ማሰብ የዋህነትና ስህተት እንደሆነ ስምም ድርጅትም ሳንጠራ በዚህ አምስት አመታት ውስጥ እንኩዋን ያየነው ይበቃል። በመሰረቱ አንድ ድርጅት ከሌላኛው ድርጅት ጋር መዋሀድ እየቻለ አላማዬንና ፕሮግራሜን ጥዬ አልዋሀድም፤ ነገር ግን በአነስተኛ ፕሮግራም ለተወሰነ ግብ ልጣመር እችላለሁ ብሎ ወደ ጥምረት ሲመጣ ከተቃራኒ ሀይል ለምሳሌ ከኢህአዴግ በፕሮግራሙ ላይ የሰፈረውን አላማ ሊያሳካ የሚችል የተሻለ እድል ከተሰጠው ጥምረቱን ጥሎ ወደዚያ የማይሄድበት ምክንያት የለም። ስለዚህ የመተማመን ጥምረት አይሰራም። ይሄ ስለግለሰቦች አይደለም። ይሄ ስለብርሀኑና ነአምን ዘለቀ አይደለም። ስለግለሰቦችም ቢሆን ሀይሉ ሻውልንና ልደቱ አያሌውን አይተናል። ግዛቸው ሽፈራውንና መስፍ ወልደማርአምን አይተናል። ነአምን ዘለቀ ወይንም ዶ/ር ብርሀኑ የሆነ ነገር አድርገው ጥምረቱን ያፈርሱታል አይደለም ስጋቴ። ቀድሞውንስ ነገር ነአምንና ብርሀኑ ውህደት እንጂ ጥምረት ውስጥ ምን ዘፈቃቸው? ከሆነ ይቅናችሁ ግን አይመስለኝም። ጥምረት አይደለም የሚያስፈልገን፡ ውህደት ነው። ከዚያ ትንሽ ድፍረት።


--------------------------------------------------------------------------------

ልጅ ተክሌ ቫንኩቨር፡ ካናዳ፡ ነሀሴ 2002/2010

[1] http://timret.org/documents/press_release_Timiret_Formation_amh.pdf እና http://timret.org/documents/alliance_amh.pdf የጥምረቱን አላማ እዚህ ላይ ያገኙታል።

[2] http://www.ginbot7.org/amh_wp/?p=762

Somaliland: Eritrean Trained ONLF Rebels Surrounded

HARGEISA (Somalilandpress) — Somaliland’s top generals said on Tuesday they have surrounded up to 300 rebel forces from neighboring Ethiopia who recently arrived in Somaliland from Eritrea.
Gen. Elmi Robleh Furrur, the general of Somaliland’s armed forces and police Commissioner Nouh Ismail Taani held a press conference in Hargeisa in which they showcased different types of weapons, military training manuals and large sums of cash that they said was seized from the Ogaden National Liberation Front. They said the group has entered the country from Northwestern shores, near the seaport towns of Zeila and Lughaya.
The two official estimated the numbers of the militia close to 250 men. General Elmi Robel Furr said that the Somaliland armed forces are surrounding the militia in Maar-maar Mountains in Awdal Region.
Although, it is not independently confirmed but the Somaliland secret and armed services believe the men are part of the Ogadan National Liberation Front. The ONLF has been engaged in brutal war against the Ethiopian government since 1984. The ONLF and the Ethiopia government have been accused of committing human right violation in the Eastern part of the country, which inhabited by Somali majority. The ONLF has been fighting to liberate Ogadan Region (Eastern part of Ethiopia) also to join the Somalia.
“A group of armed men entered Somaliland from Bulle-Adde, which is situated between the towns of Zeila and Lughaya in the North West of the country. Our information confirms that they entered the country on 10th of September. We estimated their numbers be between 250-300 men. Three large trucks were waiting for them. The group was transported in the trucks, pretending to be carrying shipments of salt. The trucks were able to pass through security checkpoints, because they were familiar to the Somaliland police in that rout in Jidh.”
Chief of Police added that:“Somaliland security services received news of abandoned artillery and ammunition found outside of Abdulqadir town near the Ethiopian borders. The army and police were able to act quickly and track the men to Maar-maar Mountains. Some of the things we recovered include 62 bazookas, chemical materials, cash (Eritrean Nakfa), communication equipments, and military training manuals in Somali and Amharic languages.”
“The militants were trying to cross into Ethiopia near the town of Abdoulqadir, however, they are surrounded in Maar-maar and Libahalaye mountains, on the western border with Ethiopia. The Ethiopia army received this information early. They were able to prevent the group from crossing into Ethiopia. We are working closely with the Ethiopian army. So the militia is now trapped between Ethiopia and Somaliland,” he revealed.

The General of armed forces, Gen. Elmi Robleh Furr said, “this is not the first time that Somaliland police captured individuals illegally entering Ethiopia through Somaliland. But this is the first time we have confronted this large number of militants, who are fully armed.”
The General added that Somaliland coast is long and vast, and Somaliland armed services and Navy cannot patrol it 100 percent. We have limited resources.
“In previous raids, we captured smuggled goods, gasoline, electronic and untaxed products; we have also captured weapons and illegal materials. We will continue our efforts to secure our borders, but as it now, we are under resourced.”
Somaliland army sent reinforcement to Abdulqadir town to captured the armed men. The General confirmed that all the evidences point to ONFL.
The two officials discounted public speculations that the armed men are part of local Somaliland militia from Awdal Regions. The newly elected Somaliland government is unpopular in Awdal Province. There were number of protests in the region after President Mohamed Ahmed Mohamoud ‘Silanyo’ announced his cabinet. Local leaders in the region were unhappy with the representation they received in the cabinet.
The Ethiopian and Somaliland government have close military and security cooperation. In previous incidents the Somaliland government handed over members of ONLF and Islamists activities wanted by the Ethiopian government. In 2008 Human Rights Watch accused the Ethiopian soldiers of committing war crimes and crimes against humanity during a counterinsurgency campaign in its Eastern Somali region. In May of this year, the Ethiopian government entered Somaliland borders to crush SSC militia and other Islamist militia.
The SSC (Sool, Saanag and Cyan) is fighting Sin ool and Snaag Regions against the Somaliland government. They are backed by pro-Somalia elements and other militants in the region such as ONLF. Ethiopia has accused groups like the ONLF, al-Shabab and SSC to be proxy for Eritrea, the regional and historic enemy of Ethiopia.
Many analysts have accused both countries to play a proxy war in Somalia. Eritrea supports number of anti-Ethiopian militant group like ONLF and al Shabab, whereas the Ethiopian government supports the weak Transitional Federal Government in Mogadishu. Both government have openly supported opposing political sides inside Somalia. The two countries have a long history of border dispute.
Written by Abdiqani Baynah and Mohamed Gulaid

Source: http://somalilandpress.com/somaliland-eritrean-trained-onlf-rebels-surrounded-18254

Sunday, September 12, 2010

Happy New Year Birtukan Invictus (Unconquered)!

Alemayehu G. Mariam
Professor of political science, CSU San Bernardino

The great Nelson Mandela said, "In my country we go to prison first and then become President." He assured the masters of the apartheid system, "You may succeed in delaying, but never in preventing the transition of South Africa to a democracy." On the occasion of the Ethiopian New Year (2003) celebrated on September 11, I contemplate the words of Mandela as I admiringly think of Birtukan Midekssa, (Ethiopia's No. 1 political prisoner and first ever political party leader), and the prospects of Ethiopia's eventual transition from dictatorship to democracy.
In December 2008, Birtukan's "pardon" from a kangaroo court conviction was revoked and her life sentence reinstated. She was literally snatched from the streets and thrown in solitary confinement for six months, despite a court ruling that such punishment was a violation of her constitutional rights.She is denied access to visitors except for her aging mother and five-year old daughter, despite a court order granting her visitor access without restrictions.She has been the object of ridicule by dictator-in-chief Meles Zenawi who has characterized her as a "chicken" who did herself in and an idle prisoner sitting around and "putting on weight".
Mandela said, "Prison itself is a tremendous education in the need for patience and perseverance. It is above all a test of one's commitment." It is comforting to know that Birtukan is receiving "a tremendous education" at Kality "Unversity" Federal Prison where she continues to face daily humiliation, isolation, degradation and dehumanization. But Birtukan perseveres and shall certainly overcome. To paraphrase William Ernest Henley's poem "Invictus" (Unconquered), for nearly two years Birtukan has been shackled in Zenawi's "pit of wrath and tears" and faced the "horror" of solitary confinement and degradation without "wincing or crying out loud." Her "head has been bloodied, but unbowed." Though she faces the "menace of the years" in prison, she remains unafraid because she is the "mistress of her fate and the captain of her soul."
It was in prison that Mandela realized the true meaning of freedom:
It was during those long and lonely years that my hunger for the freedom of my own people became a hunger for the freedom of all people, white and black. I knew as well as I knew anything that the oppressor must be liberated just as surely as the oppressed. A man who takes away another man's freedom is a prisoner of hatred, he is locked behind the bars of prejudice and narrow-mindedness. I am not truly free if I am taking away someone else's freedom, just as surely as I am not free when my freedom is taken from me. The oppressed and the oppressor alike are robbed of their humanity.
The Prisoner of the Prisoners of Hate, Prejudice and Narrow-Mindedness
It is remarkable how Birtukan's views mirror Mandela's. In all of my conversations with her during her visit to the U.S. in the Fall of 2007, (when she led the official delegation of the Coalition of Unity and Democracy [Kinijit]), her Mandela-like compassion and understanding of her jailors and tormentors was instructive and humbling. Like Mandela, Birtukan has steely resolve and unflinching commitment to the rule of law, democracy and human rights. But her political convictions never overpowered her deep compassion for others, including those who continue to mistreat and abuse her. Like Mandela who showed good will to the apartheid masters, Birtukan also shows genuine empathy and understanding for the ruthless dictators who are themselves "locked behind the bars of prejudice and narrow-mindedness". Like Mandela, that makes Birtukan one of the most unique prisoners on the planet: A prisoner of the prisoners of hatred, prejudice and narrow-mindedness. Like Mandela, Birtukan understands that she must first free the prisoners of hatred, prejudice and narrow-mindedness before she can free herself or her country.
Like Mandela, Birtukan also hungers for freedom. Her hunger for freedom is not just for herself; it is for the freedom of all the Ethiopian people regardless of ethnicity, language, religion and region. Above all, she knows all too well "that the oppressor must be liberated just as surely as the oppressed."
My New Year's Resolution
It is customary in free societies to make resolutions for the new year. Accordingly, I pledge to continue to call attention and raise awareness of Birtukan's unjust imprisonment in the court of world opinion, unceasingly continue to demand her release and the release of all political prisoners in Ethiopia, and urge all freedom-loving people throughout the world to do whatever they can to help secure the release of all political prisoners in Ethiopia.
I am sure that Birtukan's captors will snicker and giggle at the very idea of releasing her from prison. After all they have declared her release to be a "dead issue." It does not matter if they giggle or heehaw; the truth about her unjust imprisonment and abject prison conditions will be told and re-told a million times to the world. I also do not believe that prisoners of hatred, prejudice and narrow-mindedness have the moral capacity or basic human decency to set Birtukan or any other prisoner free. Only the "truth shall set her free"; and if Birtukan were to read my words here, she would gently correct me and say: "The truth shall set them free too from nineteen years of solitary confinement behind the locked steel bars and stone walls of hatred, prejudice and narrow-mindedness".
MELKAM ADIS AMET! HAPPY NEW YEAR! Our Great Sister and Ethiopia's First Daughter Birtukan Invictus (Ayibegere)! The truth shall set you free!
FREE BIRTUKAN MIDEKSSA AND ALL POLITICAL PRISONERS IN ETHIOPIA.

Follow Alemayehu G. Mariam on Twitter: www.twitter.com/pal4thedefense

Saturday, September 4, 2010

Somalia: Al-Shabaab receives weapons supply from Eritrea

Eritrea which strongly opposes the government of Somalia has delivered weapon to Al-Shabaab in southern Somalia.
MOGADISHU (Sunatimes) A plane carrying weapon supply has landed on friday morning at the airport of Kismaayo town of southern Somalia which is under the control of Al-Shabaab militant group, local residents told Sunatimes.

Militant officials belonging to Al-Qaeda were said to have been following the plane as all the roads in and out of the airport were sealed off by heavily armed Al-Shabaab militias during the unloading the weapons.

Reports close to Al-Shabaab officials said the plane flew from Eritrea which supports the Islamic rebel movements in Somalia.

Al-Shabaab (means youth in Arabic) - which controls much of southern Somalia - is now involving in what they called all-out-war against the weak government and its back up African peacekeeping troops.


Source: Sunatimes.com
info@sunatimes.com